settings icon
share icon
ጥያቄ፤

መነጠቅ መቼ ነው የሚሆነው፣ ከበታላቁ መከራ መነጠቅ ጋር በተያያዘ?

መልስ፤


የመነጠቅ ጊዜ ጉዳይ ከታላቁ መከራ ጋር በተያያዘ አንደኛው እጅግ አወዛጋቢው ጉዳይ ነው፣ ዛሬ በቤተ ክርስቲያን። ሦስቱ ዋነኛ አመለካከቶች ቅድመ-ታላቁ መከራ (ከታላቁ መከራ በፊት የሚሆን መነጠቅ)፣ ማዕከላዊ ታላቁ መከራ (በታላቁ መከራ መሀከል ወይም በዚያ አካባቢ የሚሆን ታላቁ መከራ)፣ እና ድኅረ-ታላቁ መከራ (በታላቁ መከራ መጨረሻ ላይ የሚሆን መነጠቅ) ናቸው። አራተኛው አመለካከት፣ ከቁጣ-በፊት በሚል ይታወቃል፣ ይህም ከማዕከላዊ ታላቁ መከራ አቋም መጠነኛ ማሻሻያ ያለው ነው።

በመጀመሪያ፣ የመከራውን ዓላማ መገንዘብ ጠቃሚ ነው። እንደ ዳንኤል 9፡27 ሱባዔ “ሰባት” (ሰባት ዓመት) አለ፣ ይህም ገና የሚመጣ ነው። የዳንኤል አጠቃላይ ትንቢት፣ የሰባ ሰባቶች (ዳንኤል 9፡20-27) የሚናገረው ስለ እስራኤል ሕዝብ ነው። እሱም፣ እግዚአብሔር አትኩሮቱን በተለይ በእስራኤል ላይ የሚያደርግበት ጊዜ ነው። የሰባት ሱባኤ መከራ የግድ መሆን ያለበት እግዚአብሔር ከእስራኤል ጋር በተለይ የሚያደርገው ነው። ይህም ማለት ቤተ ክርስቲያን አትኖርም ማለትን አያመለክትም፣ ቤተ ክርስቲያን በዛን ሰዓት በምድር ላይ ለመኖሯ ጥያቄ ያስነሣል እንጂ።

ቀዳሚው የመነጠቅ ምንባብ በቅዱስ ቃሉ ውስጥ 1 ተሰሎንቄ 4፡13-18 ነው። እሱም የሚያስረግጠው በሕይወት ያሉት አማኞች ሁሉ፣ ከሞቱት አማኞች ጋር፣ ጌታ ኢየሱስን በአየር እንደሚቀበሉትና ለዘላለም ከእሱ ጋር እንደሚሆኑ ነው። መነጠቅ እግዚአብሔር የራሱን ሕዝብ ከምድር ላይ የሚወስድበት ነው። ከጥቂት ቁጥሮች በኋላ፣ በ1 ተሰሎንቄ 5፡9፣ ጳውሎስ ይላል፣ “እግዚአብሔር ለቁጣ አልመረጠንምና፣ ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ደኅንነትን ለመቀበል እንጂ።” የራዕይ መጽሐፍ በቀዳሚነት ስለ ታላቁ መከራ ጊዜና ሰዓት በቀዳሚነት የተናገረ፣ ትንቢታዊ መልእክት ነው፣ እግዚአብሔር ቁጣውን በምድር ላይ እንዴት እንደሚያፈስ፣ በታላቁ መከራ ጊዜ። እሱም የማይጣጣም ይመስላል፣ እግዚአብሔር አማኞች ቁጣውን እንደማይቀበሉና ቀጥሎም በታላቁ መከራ ይሣቀዩ ዘንድ በምድር ላይ የሚተዋቸው። ሐቁ፣ እግዚአብሔር ክርስቲያኖችን ከቁጣ ለማዳን የሰጠው ተስፋ ባጭሩ የራሱን ሕዝብ ከምድር ላይ ለመውሰድ ቃል የገባው እነዚያን ሁለት ሁነቶች አያይዞ ለማስኬድ ይሆናል።

ሌለኛው የመነጠቅ ጊዜ ወሳኝ አንቀጽ ራዕይ 3፡10 ነው፣ ይሄውም ክርስቶስ አማኞችን “ከፈተና ሰዓት” ሊያድናቸው ቃል የገባበት፣ በምድር ላይ ሊሆን ካለው። ይህ ሊሆን የሚችለው ሁለት ነገሮች ነው። አንድም፣ ክርስቶስ አማኞችን በፈተና መሐል ሊጠብቃቸው መቻሉን፣ ወይም አማኞችን ከፈተና መሐል ሊያወጣ መቻሉን ነው። ሁለቱም ሁነኛ ትርጉም ይኖራቸዋል፣ ከግሪኩ ቃል ትርጉም “ከ” የተነሣ። ሆኖም፣ አማኞች ከምን እንደሚጠበቁ ተስፋ እንደተሰጠ መገንዘብ ጠቃሚ ነው። እሱ ፈተና ብቻ አይደለም፣ ግን የፈተና “ሰዓት” ነው። ክርስቶስ አማኞችን ሊጠብቅ ቃል ገብቷል፣ ፈተና ካለባቸው ሁነኛ ጊዜና ሰዓት፣ እሱም ታላቁ መከራ ተብሎ የሚታወቀው። የታላቁ መከራ ዓላማ፣ የመነጠቅ ዓላማ፣ የ1 ተሰሎንቄ 5፡9 ፍቺ፣ እና የራዕይ 3፡10 ትርጓሜ ሁሉ ግልጽ የሆነ ድጋፋቸውን የሚሰጡት ለቅድመ-ታላቁ መከራ አቋም ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በጥሬውና በቋሚነት ከተተረጎመ፣ ቅድመ-ታላቁ መከራ አቋም እጅግ የተሻለው መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው ትርጓሜ ነው።

English



ወደ አማርኛ መነሻ ገጽ ለመመለስ

መነጠቅ መቼ ነው የሚሆነው፣ ከበታላቁ መከራ መነጠቅ ጋር በተያያዘ?
© Copyright Got Questions Ministries