settings icon
share icon
ጥያቄ፤

በክርስትና ሕይወቴ ኃጥአትን እንዴት ማሸነፍ እችላለሁ?

መልስ፤


በጥረታችን ኃጥአትን ለማሸነፍ ይረዳን ዘንድ መጽሐፍ ቅዱስ ብዙ የተለያዩ መንገዶችን ያቀርባል፡፡ በዚህ ዕድሜ በኃጥአት ላይ ፍጽሞ በሚገባ ባለድል አንሆንም (1ኛ ዮሐንስ 1፡8)፤ ነገር ግን ያ አሁንም የእኛ ግብ ሊሆን ይገባል፡፡ በእግዚአብሔር ዕርዳታ እና የቃሉን መርሆች በመከተል በሂደት ኃጥአትን ማሸነፍ እና በበለጠ ክርስቶስን መምሰል እንችላለን፡፡

በጥረታችን ኃጥአትን ለማሸነፍ መጽሐፍ ቅዱስ የሚጠቅሰው የመጀመሪያው መንገድ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ሰጥቶናል ስለዚህም በክርስትና ህይወታችን ባለድል መሆን እንችላለን፡፡ እግዚአብሔር ወደ ገላትያ ሰዎች 5፡16-25 ውስጥ የሥጋ ሥራዎችን ከመንፈስ ፍሬዎች ጋር ያነጻጽራል፡፡ በዚያ ምንባብ ውስጥ በመንፈስ እንድንሄድ ተጠርተናል፡፡ ሁሉም አማኞች አስቀድሞ መንፈስ ቅዱስ አላቸው፤ ነገር ግን ይህ ምንባብ ለእሱ ቁጥጥር እየተገዛን በመንፈስ መሄድ እንደሚገባን ይነግረናል፡፡ ይህ በቋሚነት መንፈስ ቅዱ በህይወታችን ውስጥ ሥጋን ከመከተል ይልቅ በተከታታይ የመንፈስ ቅዱስን ምሪት መከተል መምረጥ ማለት ነው፡፡

መንፈስ ቅዱስ ማድረግ የሚችለው ልዩነት፤ በመንፈስ ቅዱስ ከመሞላቱ በፊት ኢየሱስን ሦስት ጊዜ በካደው በጴጥሮስ ህይወት ታይቷል፤ እናም ከዚህ በኋላ ክርስቶስን እስከሞት ድረስ እንደሚከተለው ተናግሮ ነበር፡፡ በመንፈስ ከተሞላ በኋላ በጴንጤቆስጤ በዓል ላይ በአደባባይ በድፍረት ለአይሁዶች ነገራቸው፡፡

የመንፈስን ምሪት ላለማጥፋት ለመሞከር በመንፈስ እንሄዳለን (በ1ኛ ተሰሎንቄ 5፡19 እንደተነገረው) እና በምትኩ በመንፈስ መሞላትን እንፈልግ (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5፡18-21)፡፡ አንድ ሰው በመንፈስ ቅዱስ እንዴት ይሞላል? በብሉይ ኪዳን ውስጥ እንደነበረው ከሁሉ በፊት የእግዚአብሔር ምርጫ ነው፡፡ እሱ እንዲከወን የፈለገውን ሥራውን የሚያስፈፅሙ ግለሰቦችን መረጠ እና በመንፈሱም ሞላቸው (ኦሪት ዘፍጥረት 41፡38፤ ኦሪት ዘፀአት 31፡3፤ ኦሪት ዘዳግም 24፡2፤ 1ኛ ሳሙኤል 10፡10) በእግዚአብሔር ቃል ራሳቸውን እየሞሉ ያሉትን እነዚያን ሊሞላቸው እንደሚመርጥ ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5፡18-21 እና ወደ ቆላስያስ ሰዎች 3፡16 ውስጥ ማረጋገጫ አለ፡፡ ይሄ ወደ ሁለተኛው መንገድ ይመራናል፡፡

የእግዚአብሔር ቃል፤ መጽሐፍ ቅዱስ፤ እግዚአብሔር ለየትኛውም በጎ ሥራ ሁሉ እኛን ለማስታጠቅ ቃሉን ሰጥቶናል ይላል (2ኛ ጢሞቴዎስ 3፡16-17)፡፡ እንዴት መኖር እንዳለብን እና ምን ማመን እንዳለብን ያስተምረናል፣ የተሳሳቱ ጎዳናዎችን በመረጥን ጊዜ ይገልጥልናል፣ ወደ ትክክለኛውም ጎዳና እንድንመለስ እና በዚያ ጎዳና እንድንቆይም ይረዳናል፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ሕያው እና የሚሰራ እንደሆነ፣ ሥር ለመስደድ ወደ ልቦቻችን ዘልቆ ለመግባት እና ጥልቅ የሆኑትን የልባችንን ኃጥአቶች እና አመለካከቶችን ማሸነፍ እንደሚችል ወደ ዕብራውያን ሰዎች 4፡12 ይነግረናል፡፡ ዘማሪው በመዝሙረ ዳዊት 119 ውስጥ ስለ እሱ የህይወት ቀያሪነቱ ኃይል በጥልቀት ይናገራል፡፡ ኢያሱ ጠላቶቹን የማሸነፍ ውጤታማነት ቁልፉ ይህንን መንገድ ያለመርሳት እንዳልሆነ ነገር ግን በምትኩ በቀን እና በማታ ማሰላሰል እና እሱን መታዘዝ እንደሆነ ተነግሮታል፡፡ እግዚአብሔር ባዘዘ ጊዜ እንኳ በውትድርናው ስሜት የማይሰጥ ነገር ባይሆንም ይህን አደረገ፤ እና ይሄ ለተስፋይቱ ምድር ላደረገው ጦርነት የድሉ ቁልፍ ነበር፡፡

እኛ ራሳችን ብዙውን ጊዜ በቀላሉ የምናየው መንገድ መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ ወደ ቤተክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱሶቻችንን በመሸከም ወይም የቀን ጥሞና ወይም በቀን አንድ ምዕራፍ እያነበብን ምልክታዊ አገልግሎት እንሰጣለን፣ነገር ግን እሱን ማሰቡን ፤ እሱን ማሰላሰሉን ወይም በኑሮዎቻችን ላይ ተግባራዊ ማድረጉን ትተናል፣ እሱ የሚገልጣቸውን ኃጥአቶቻችንን መናዘዝ ወይም ለእኛ ለሚገልጣቸውን ስጦታዎች እግዚአብሔርን ማመስገን ትተናል፡፡ ወደ መጽሐፍ ቅዱስ በሚመጣበት ጊዜ እኛ ብዙውን ጊዜ ምግብ ያስጠላቸው ወይም አመጋገባቸው የተዛባብን ነን፡፡ ከቃሉ በመመገብ በመንፈሳዊው እንዲያው በህይወት እንዲያቆየን ያህል (ነገር ግን ጤናማ እና የሚፋፉ ክርስቲያኖች እንድንሆን ፈጽሞ የሚበቃንን ያህል አንበላም) ወይም ብዙ ጊዜ ልንመገብ እንመጣለን ነገር ግን መንፈሳዊ ምግብን ከእሱ ለማግኘት ለረጅም ጊዜ በፍጹም አናሰላስለውም፡፡

እሱ ጠቃሚ ነው፣የእግዚአብሔርን ቃል በየቀኑ የማጥናትና የማሰላሰል ልምድ ካላደረግህ ያን ማድረግ ትጀምራለህ፡፡ ጥቂቶች የሚረዳ ጅማሬ ሆኖ አግኝተውታል፡፡ ከእሱ ያገኘኸውን አንድ ነገር እስከምትጽፍ ድረስ ቃሉን ላለመተው ልምድ አድርገው፡፡ ጥቂቶች እነርሱን በተናገራቸው ዙሪያ ይለወጡ ዘንድ እንዲረዳቸው በመጠየቅ ወደ እግዚአብሔር የሚደረጉትን ፀሎቶች ይመዘግባሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በሕይወታችን ውስጥ መንፈስ የሚጠቀምበት መሳሪያ (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6፡17)፤ እግዚአብሔር መንፈሳዊ ውጊያዎቻችንን እንድንዋጋ የሰጠን ጠቃሚ እና ዋነኛ የጦር ዕቃ አካል (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6፡12-18) ነው፡፡

በኃጥአት ላይ ለምናደርጋቸው ውጊያዎቻችን ሦስተኛው ዋነኛ መንገድ ፀሎት ነው፡፡ አሁንም ብዙውን ጊዜ ክርስቲያኖች የከንፈር አገልግሎት የሚሰጡበት መንገድ ነው ነገር ግን ጥቅሙን ደካማ ያደርጋል፡፡ የፀሎት ስብሰባዎች፣ የፀሎት ጊዜያቶች ወ.ዘ.ተ. አሉን ነገር ግን ጸሎትን የጥንቷ ቤተክርስቲያን በምትጠቀምበት መንገድ አልተጠቀምንበትም (የሐዋርያት ሥራ 3፡1፣4፡31፣6፡4፣13፡1-3)፡፡ ጳውሎስ ያገለግላቸው ለነበሩት እንዴት ይፀልይ እንደነበር በተደጋጋሚ ይጠቅሳል፡፡ እግዚአብሔር ጸሎትን በተመለከተ የሚያስደንቁ ተስፋዎችን ሰጥቶናል (የማቴዎስ ወንጌል 7፡7-11፣ የሉቃስ ወንጌል 18፡1-8፣ ዮሐንስ ወንጌል 6፡23-27፣ 1ኛ ዮሐንስ መልዕክት 5፡14-15)፣ እና ጳውሎስ ለመንፈሳዊ ውጊያ በመዘጋጀት ምንባቡ ውስጥ ፀሎትን ያካትታል (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6፡18)፡፡

በኑሮዎቻችን ኃጥአትን በማሸነፉ ፀሎት እንዴት ጠቃሚ ነው? ልክ ከጴጥሮስ ክህደት በፊት በጌተሰማኔ የአትክልት ሥፍራ ለጴጥሮስ የክርስቶስ የሆኑ ቃላቶች አሉን፡፡ ኢየሱስ እየጸለየ ጴጥሮስ እየተኛ ነው፡፡ ኢየሱስ አነቃውና እናም አለው “ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው።”(የማቴዎስ ወንጌል 26፡41) እኛ እንደ ጴጥሮስ ትክክል የሆነውን ማድረግ እንፈልጋለን ነገር ግን ጥንካሬውን እያገኘን አይደለም፡፡ መፈለጋችንን ፣ ማንኳኳታችንን፣ መጠየቃችንን ለመቀጠል የእግዚአብሔርን ተግሳጽ መከተል ያስፈልገናል እናም ያ የምንፈልገውን ጥንካሬ ይሰጠናል (የማቴዎስ ወንጌል 7፡7)፡፡ ጸሎት ምትሃታዊ ዘይቤ አይደለም፡፡ ጸሎት በቀላሉ የእኛን የራሳችንን ድክመትና የእግዚአብሔርን የማይወሰነውን ኃይል ማረጋገጥ እና እኛ ማድረግ የምንፈልገውን ሳይሆን እሱ እንድናደርገው የሚፈልገውን ለማድረግ ለዚያ ጥንካሬ ወደ እሱ መዞር ነው (1ኛ ዮሐንስ መልዕክት 5፡14-15)

ኃጥአትን ለመማረክ በምናደርገው ጦርነታችን ውስጥ አራተኛው መንገድ፤ የሌሎች አማኞች ህብረት፤ ቤተክርስቲያን ነው፡፡ ኢየሱስ ደቀመዛሙርቱን በላከበት ጊዜ ሁለት ሁለት አድርጎ ላካቸው (የማቴዎስ ወንጌል 10፡1)፡፡ በሐዋርያት ሥራ ውስጥ ያሉ ሚሲዮኖች በአንድ ጊዜ አንድ ሆነው አልወጡም ነበር ነገር ግን ሁለት ወይም ከዚያ በላይ በሆነ ማህበር ነበር፡፡ ኢየሱስ አንድ ላይ መሰብሰባችንን እንዳንተው ነገር ግን ያን ጊዜ በፍቅር እና በመልካም ሥራዎች እርስ በራሳችንን ለማበረታታት እንድንጠቀምበት አዞናል (ወደ ዕብራውያን ሰዎች 10፡24)፡፡ አንዳችን ለአንዳችን ስህተታችንን እንድንናዘዝ ይነግረናል (የያዕቆብ መልዕክት 5፡16) በብሉይ ኪዳን በጥበብ መጽሐፍ ውስጥ ብረት ብረትን እንደሚስል ተነግሮናል፥ ስለዚህ አንድ ሰው ሌላውን ይስላል (መጽሐፈ ምሳሌ 27፤17)። በቁጥሮች ውስጥ ጥንካሬ አለ (መጽሐፈ መክብብ 4፡11-12)፡፡

ብዙ ክርስቲያኖች የሚከብዱ ኃጥአቶችን በማሸነፉ ረገድ ኃላፊነትን የሚወስድ ወዳጅ መኖር በጣም ትልቅ ጥቅም መሆን እንደሚችል ያን አግኝተዋል፡፡ ከአንተ ጋር ሊያወራ፤ ሊፀልይ፣ ሊያበረታታህ፤ እና እንዲያውም የሚገጽህ የሚችል ሌላ ሰው ማግኘት ትልቅ ዋጋ አለው፡፡ ፈተና ለሁላችንም ያለ ነው (1ኛ ቆሮንቶስ 10፡13) ኃላፊነትን የሚወስድ ወዳጅ ወይም ኃላፊነትን የሚወስድ ማህበር መኖሩ እንዲያውም በጣም ከባድ የሆኑትን ኃጥአቶችን ለማሸነፍ የሚያስፈልገንን የመጨረሻውን የማበረታቻ እና የመነሳሳት መጠን ሊሰጠን ይችላል፡፡

አንዳንድ ጊዜ በኃጥአት ላይ ድል መንሳት በፍጥነት ይመጣል፡፡ ሌላ ጊዜ ድል በጣም በዝግታ ይመጣል፡፡ እግዚአብሔር የእሱን መንገዶች ስንጠቀም ለውጥን በህይወታችን በሂደት እንደሚያመጣ ቃል ገብቷል፡፡ ኃጥአትን ለማሸነፍ ጥረታችንን በቀጣይነት መቀጠል እንችላለን ምክንያቱም እሱ በቃሉ ታማኝ እንደሆነ እናውቃለን፡፡

English



ወደ አማርኛ መነሻ ገጽ ለመመለስ

በክርስትና ሕይወቴ ኃጥአትን እንዴት ማሸነፍ እችላለሁ?
© Copyright Got Questions Ministries