settings icon
share icon
ጥያቄ፤

ከምድር ወጪ ያሉ ልዩ ፍጥረታት አሉ?

መልስ፤


በመጀመሪያ ከምድር ውጪ ያሉ (aliens) ‹‹የሞራል ምርጫን መምረጥ መቻል፤ እውቀት ስሜት ፈቃድ መኖር›› በማለት ትርጓሜ እንስጥ፡፡ በቀጠል ሳይንሳዊ እውነታዎች፡-

1.ሰዎች መንኮራኩሮችን በቅርቡ በእያንዳንዱ በስርዓተ ጸሐይ ባሉ ፐላኔት ልከዋል፡፡ እነዚህን ፕላኔቶች ከተመለከቱ በኋላ ሁሉንም ተቆጣጠርናቸው ግን ማርስ ምናልባት የጁፒተር ጨረቃ ህይወት እንዲቀጥል እየረዳች ነው፡፡

2.በ1976 ዩ.ኤስ.ኤ ሁለት አብራሬዎችን ወደ ማርስ ላከች፡፡ እያንዳንዳቸው ሞቆፈር የሚያስችላቸው መሳሪያ አላቸው እና ስለ ህይወት የሆነ ምልክት ያስተዋሉ እነደሆነ ቆፈሩ፡፡ ምንም አላገኙም፡፡ በአንጻሩ አፈር ማፍራተ ከማይችለው የምድር በረሃ ካገኛችሁ ወይንም በጣም ከሚቀዘቅዘው አንታርቲካ ያኔ የረቂቅ ነፍሳት ክምችት ታገኛላችሁ፡፡ በ1997 አሜሪካኖች ወደ ማርስ የጦር አይሮፕላኖችን ላከች፡፡ እነዚህ አሳሾች በዙ የምርመራ ናሙናዎችን ላኩ፡፡ እንዲሁም ምንም ህይወት የሚባል ነገር እንደሌለ አረጋገጡ፡፡ ከዛን ጊዜ ጀምሮ ወደ ማርስ ብዙ ጉዞዎች ተደርገዋል፡፡ ውጤቱ ግን ተመሳሳይ ነው፡፡

3.የስነከዋክብት አጥኚዎች በየጊዜው አዳዲስ ፕላኔቶችን ከጸሐይ ርቀው ያገኛሉ፡፡ አንዳንዶች እንደሚገምቱት የብዙ ፕላኔቶች መኖር የሚያረጋግጠው ህይወት በዩኒቨርስ ውስጥ አንድ ቦታ ሊኖር እንደሚችል ነው፡፡ እውነታው ከእነዚህ የትኛውም ቢሆን ህይወት ያለበት ፕላኔት መሆኑን የሚደግፍ ሆኖ ያልተረጋገጠ መሆኑ ነው፡፡ እጅግ ሰፊ የሆነው በመሬትና በእነዚህ ፕላኔቶች መካከል ያለው ርቀት ህይወት ሊኖርባቸው ይችላል የሚለውን ግምት ላማስቀመጥ የማይቻል ያደርገዋል፡፡ ምድር ብቻ በስርዓት ፀሐይ ውስጥ የህይወትን መኖር የምትፈቅድ መሆኑን እያወቁ ዝግመተ ለውጥ ደጋፊዎች በከፍተኛ ሁኔታ ሌላ ፕላኔት በሌላ ስርዓተ ፀሐይ ህይወት ሊኖር ይችላል የሚለውን የአመለካከት ዝንባሌ ለመደገፍ ይፈልጋሉ፡፡ ሌሎች ብዙ ፕላኔቶች አሉ ስለ እነርሱ ግን የህይወትን መኖር ሊቀበሉ እንደሚችሉ ብዙ አናውቅም፡፡

ሰለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ምንድን ነው የሚለው? ምድር እና የሰው ዘር በእግዚአብሔር ፍጥረት ውስጥ የተለዩ ናቸው፡፡ ዘፍጥረት 1 እንደሚያስተምረን እግዚአብሔር ምድርን የፈጠረው ፀሐይን ጨረቃን ከዋክብት እንኳ ከመፍጠሩ በፊት ነው፡፡ ሥራ 17፡ 26፤26 እንደሚነግረን ‹‹ዓለሙንና በእርሱ ያለውን ሁሉ የፈጠረ አምላክ እርሱ የሰማይና የምድር ጌታ ነውና እጅ በሠራው መቅደስ አይኖርም፤

እርሱም ሕይወትንና እስትንፋስን ሁሉንም ለሁሉ ይሰጣልና አንዳች እንደሚጎድለው በሰው እጅ አይገለገልም።ምናልባትም እየመረመሩ ያገኙት እንደ ሆነ፥ እግዚአብሔርን ይፈልጉ ዘንድ በምድር ሁሉ ላይ እንዲኖሩ የሰውን ወገኖች ሁሉ ከአንድ ፈጠረ፥ የተወሰኑትንም ዘመኖችና ለሚኖሩበት ስፍራ ዳርቻ መደበላቸው። ቢሆንም ከእያንዳንዳችን የራቀ አይደለም።››

ሰው በመጀመሪያ ሲፈጠር ያል ኃጢያት ነበር በምድር ሁሉ ያለው እጅግ መልካም ነበር፡፡ (ዘፍ 1:31). የመጀመሪያው ሰው ኃጢያት ሲያደርግ (ዘፍ 3), ውጤቱ በሽታንና ሞትን ጨምሮ ሁሉን አቀፍ ችግር ነበር ያስከተለው፡፡ እንስሳት እግዚአብሔርን የሚበድሉ ባይሆኑም (ሞራል ያላቸው ፍጥረታት አይደሉም) እነርሱም ይሰቃያሉ ይሞታሉ፡፡ (ሮሜ 8:19-22):: ኢየሱስ እኛ በኃጢያታችን ምክንያት ልንቀበለው የሚገባንን ዋጋ ለመክፈል ሞተ፡፡ በሚመለስበት ጊዜ ከአዳም ጀምሮ የተቀመጠብንን መርገም ያነሳዋል (ራዕ 21–22):: እናስታውስ ሮሜ 8:19-22 የሚያስቀምጥልን ሁሉም ፍጥረታት ይህን ቀን በናፍቆት እንደሚጠብቁ ነው፡፡ እንደዚሁም ኢየሱስ ክርስቶስ ሊሞት እንደመጣ እንዲሁም የሚሞተው አንዴ ብቻ እንደሆነ ማስታወስ ያስፈልጋል (ዕብ 7:27; 9:26-28; 10:10).

አሁን ሁሉም ፍጥረታት ከመርገም ስር ሆነው ቢሰቃዩም የትኛውም ከምድር የተለየ ህይወት ሁሉ ይሰቃያል፡፡ ለክርክር በቻ ከሆነ የሞራል ህግ ያላቸው በምድር ላይ የኖራሉ፤ እነግዲያው እነርሱም ይሰቃያሉ እና አሁን ካልሆነ ሁሉም ነገር በታላቅ ድምጽ ሲያልፍ ሁሉም ነገር በታላቅ እሳት ሲጋዩ የሰቃያሉ (2ኛ ጴጥ 3፡9)፡፡ ኃጢያትን ፈጽሞ አድርገው ባያውቁ ኖሮ እግዚአብሔር ጻድቅ አይሆንም ነበር፡፡ ኃጢያትን ካደረጉ ግን ኢየሱስም የሚሞተው አንዴ ብቻ ከሆነ (በምድር ላይ የሞተው) እንግዲያውስ በኃጢያታቸው ይኖራሉ ይህውም ደግሞ ከእግዚአብሔር ባሕሪ ጋር የሚቃረነውን (2ጴጥ 3፡9) ይህ ምልሽ ባለገኛ ምስጢር ይተወናል አለዚያም እውነት ነው ሌሎች ሞራል ህግ ያላቸው ፍጥረታት ከምድር ውጪ የለም፡፡

በሌላው ፕላኔት የሚኖሩ ሞራል ህግ እና ሳይነስ ስሌላቸውስ አንዴት ነው? አልጌ ወይም ውሻ እና ድመት በሌላ ፕላኔት ሊገኙ ይችላሉ? እንደሚታወቀው እንግዲያውስ በየትኛውም የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ምንም የሚሆን የተለየ ክፉ ነገር የለም፡፡ ግን እንደነዚህ ያሉ ጢያቄዎችን ስንጠይቅ ማረጋገጫዎችን ሊፈልግ ይችላል‹‹ የሞራል ህግና ሳይንስ የሌላቸውን ፍጥረት በሌሎች ፕላኔት ሁለም ፍጥረት የሚሰቃይ እስከ ሆነ ድረስ እግዚአብሔር ምን አይነት እቅድ ይኖረዋል?››

በመጨረሻም መጽሐፍ ቅዱስ በሌላ የዩነቨርስ አካል ህይወት አለ ብሎ ለማመን ምንም አይነት ምክንያት አይሰጠንም፡፡ እውነት ነው መጽሐፍ ቅዱስ ሊሆን የማይችልበት ብዙ ቁልፍ ምክንያቶችን ይነግረናል፡፡ እውነት ነው ብዙ እንግዳ የሆኑ የማይጠበቁ ነገሮች ይሆናሉ፡፡ እንግዲያውስ ይህንን እውነት ባህሪ ከመድር ውጪ ላሉ ሌሎች ፍጥረታት ለመስጠት ምንም ምክንያት የለም፡፡ ለእነዚህ የግምት ክስተቶች ለይቶ ማወቅ የሚቻልበት ምክንያት ቢኖር ምንፈሳዊ ነው ሊሆን የሚችለው እና በእርግጠኝነት ከመነሻው አጋንታዊ ነው፡፡

English



ወደ አማርኛ መነሻ ገጽ ለመመለስ

ከምድር ወጪ ያሉ ልዩ ፍጥረታት አሉ? ሁልጊዜ በገንዘብ አያያዝ ብድር ስህተት ነው? ገንዘብ ማበደር ወይም መበደር ሁልጊዜም ስህተት ነው?
© Copyright Got Questions Ministries