settings icon
share icon
ጥያቄ፤

አምላክ አሁንም ተአምራትን ያደርጋል?

መልስ፤


ብዙ ሰዎች እግዚአብሔር ለእነሱ እራሱን "እንዲያረጋግጥ" ተዓምራትን እንዲያደርግ ይመርጣሉ፡፡ "እግዚአብሔር ተአምርን ምልክትን ወይም ድንቅን ቢያደርግ ኖሮ አመን ነበር!" ይህ ሐሳብ ግን በቅዱሳት መጻሕፍት ተቃራኒ ነው፡፡ አምላክ ለእስራኤላውያን አስደናቂና አስገራሚ ተዓምራትን ባደረገበት ጊዜ እርሱን እንዲታዘዙ አደረጋቸው? አላደረጋቸውም፤ እስራኤላውያን ሁሉንም ተዓምራቶች ቢያዩም አልታዘዙም እና በእግዚአብሔር ላይ ያመፁ ነበር፡፡ እግዚአብሔር ቀይ ባሕርን ሲከፍል ከተመለከቱ በኋላ እነዚያው እራሳቸው እግዚአብሔር ተስፋይቱን ምድር ነዋሪዎች ድል ማድረግ ተጠራጥረው ነበረ፡፡ ይህ እውነት በሉቃስ 16: 19-31 ተገልጧል፡፡ በታሪኩ ውስጥ በሲኦል ያለ አንድ ሰው ወንድሞቹን ለማስጠንቀቅ አብርሃም አልዓዛርን ከሞት እንዲመልሰው ጠየቀው አብርሃም ለሙሴ ነገረው, "ሙሴንና ነቢያትን የማይሰሙ ከሆነ ማንም ሰው ከሞት ቢነሳ እንኳ አያምኑም" (ሉቃስ 16:31).

ኢየሱስ ስፍር ቁጥር የሌላቸውን ተዓምራትን አድርጓል፤ ነገር ግን እጅግ ብዙ ሰዎች በእሱ አያምኑም ነበር፡፡ እግዚአብሔር ከዚህ በፊት እንዳደረገው ሁሉ ዛሬም ቢሠራ ውጤቱ አንድ ዓይነት ነው፡፡ ሰዎች ተገርመው ለአጭር ጊዜ በእግዚአብሔር ይታመናሉ፡፡ ያ እምነት ጥራዝ ነጠቅ ይሆንና ድንገተኛ ወይም አስፈሪ የሆነ ክስተት የተከሰተበትን ጊዜ ያጠፋል፡፡ በተዓምራት ላይ የተመሠረተ እምነት የጎለመሰ እምነት አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ለመዳን ታላቁን ተአምራት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር እንዲመጣ እና ለኃጢያታችን ሁሉ እንዲሞት አድርጎአል (ሮሜ 5፡8) ስለዚህ እኛ መዳን እንችላለን (ዮሐንስ 3 16)፡፡ እግዚአብሔር አሁንም ተአምራትን ያደርጋል፡፡ አብዛኛዎቹም ትኩረት ያላገኙ ወይንም የተካዱ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ተጨማሪ ተዓምራቶች አያስፈልጉንም፡፡ የሚያስፈልጉን ነገሮች በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን በመዳን ድነት ማመን ነው፡፡

ተአምራቶች ዓላማቸው ተአምራቱን የፈፀመውን ማረጋገጥ ነው፡፡ የሐዋሪያት ሥራ 2:22 እንዲህ ይላል፡-‹‹የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ይህን ቃል ስሙ፤ ራሳችሁ እንደምታውቁ፥ የናዝሬቱ ኢየሱስ እግዚአብሔር በመካከላችሁ በእርሱ በኩል ባደረገው ተአምራትና በድንቆች በምልክቶችም ከእግዚአብሔር ዘንድ ለእናንተ የተገለጠ ሰው ነበረ፤›› የሐዋርያቱም ከዚሁ ጋር ተመሳሳይ ነው ‹‹በእርግጥ የሐዋርያነት ምልክት በመካከላችሁ በምልክትና በድንቅ ነገር በተአምራትም በሁሉ ትዕግሥት ተደረገ።›› (2 ኛ ቆሮንቶስ 12 ፡12). ስለወንጌል ሲናገሩ ዕብራውያን ምዕራፍ 2 ቁጥር 4፡- ‹‹እግዚአብሔርም እርሱ ራሱ እንደ ፈቀደ በምልክትና በድንቅ ነገር በልዩ ልዩ ተአምራትም፥ መንፈስ ቅዱስንም በማደል አብሮ መሰከረለት፡፡›› በማለት ይናገራል፡፡ አሁን በቅዱሳት መጻሕፍት የተመዘገበው የኢየሱስ እውነት አለ፡፡ አሁን በቅዱሳት መጻሕፍት የተመዘገቡት የሐዋርያት ጽሑፎች አሉን፤ ኢየሱስና ሐዋርያቱ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተመዘገበው የእምነታችን የማእዘን ድንጋይ እና መሠረት ናቸው (ኤፌሶን 2፡20)፡፡ በዚህ መሠረት የኢየሱስ እና የእርሱ ሐዋርያት በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ትክክለኛነቱን ትክክለኛ በሆኑት ቅጂዎች እንደተረጋገጡ ሁሉ ተአምራት አያስፈልጉም፡፡ አዎን እግዚአብሔር አሁንም ተአምራትን ያደርጋል፡፡ በተመሳሳይም በጥንት ዘመን እንደነበሩት ሁሉ ተዓምራቶች ዛሬም እንደሚከሰቱ መጠበቅ አይኖርብንም፡፡

English



ወደ አማርኛ መነሻ ገጽ ለመመለስ

አምላክ አሁንም ተአምራትን ያደርጋል? ሁልጊዜ በገንዘብ አያያዝ ብድር ስህተት ነው? ገንዘብ ማበደር ወይም መበደር ሁልጊዜም ስህተት ነው?
© Copyright Got Questions Ministries